የጥምቀት በዓል በሊድስ

Jan 19, 2025 at 04:20 PM

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን::

እንኳን ለጌታችን  ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 

 ነገ ጥር10 እና እሁድ11/2017 (January18-19 /2025)  የዘንድሮን 2017 ዓምየጥምቀት በዓልን በደብራችን በሊድስ ደብረ ስብሐት መድኃኔዓለም ቤተክርስትያን የደብረ  ደብረ ፀሀይቅድስት ኪዳነ ምህረት   የደብረ ፀሀይ ቅዱስ ጊዮርጊስ  በጋራ በመሆን በታላቅ ድምቀት ይከበራል::

ነገ ቅዳሜ ጥር 10/2017 (Jan 18/2025 ) ከሰባቱ አጿማት አንዱ ፆመ ገሀድ መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም በግዴታ የምንፆመው  መሆኑን እንድታውቁ  እያሳሰብን 

የከተራ መርሀግብሩ የሚጀምረዉ 4;30pm ሲሆን የሌሊቱ ማህሌት  12:00 ;Midnight )ይጀመራል፤ ቅዳሴ 4;30 am ሥርዓተ ጥምቀቱ  የቅዳሴው ፀሎት እንደተጠናቀቀ ይከናወናል::

 መልካም በአል
የደብሩ ጽሕፈት ቤት